Latest

ቤተ ክርስቲያኗ ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ላመጡት እርቅና ሰላም ልዩ ሽልማት አበረከተች


(ኤፍ.ቢ.ሲ) የኢትዮጵያ ኦርቶዶክስ ተዋህዶ ቤተ ክርስቲያን ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድና ቀዳማዊት እመቤት ዝናሽ ታያቸው በኢትዮጵያና ኤርትራ መካከል ላመጡት ሰላምና እርቅ ልዩ ሽልማት አበረከተች።

ቤተ ክርስቲያኗ ልዩ ሽልማቱን ያበረከተችው ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ በኢትዮጵያ እና በኤርትራ መካከል ብሎም በምስራቅ አፍሪካ ቀጠና ሰላም እንዲመጣ አድርገዋል በሚል ነው።

ጠቅላይ ሚኒስትር ዶክተር አብይ አህመድ ሽልማቱን በተረከቡበት ወቅትም፥ ሽልማቱ ያለእረፍት ይህ ነገር እንዲመጣ ሲታገሉ ለነበሩ እና ይህ ለውጥ እንዲመጣ ሲፀልዩ የነበሩትን በሙሉ የሚገባ ነው ማለታቸውን የጠቅላይ ሚኒስትር ጽህፈት ቤት ልዩ ሀላፊ አቶ ፍፁም አረጋ በትዊተር ገጻቸው አስታውቀዋል።

በሙለታ መንገሻ

No comments