Latest

በራያ እና አካባቢው የሰላም ጉዳይ ላይ በክቡር ጠቅላይ ሚንስትሩ መሪነት ውይይት ተደርጓል

ጠቅላይ ሚንስትሩ

አቶ ፍፁም አረጋ እንደገለፁት ክቡር ጠቅላይ ሚንስትር ዶ/ር አብይ አህመድ በዛሬው ዕለት ከክቡር ምክትል ጠቅላይ ሚንስትሩ ከአቶ ደመቅ መኮንን: ከኢፌዴሪ የህዝብ ተወካዮች ምክር ቤት እና የፌዴሬሽን ምክር ቤት አፈ-ጉባኤዎች እንዲሁም ከሁለቱ ክልሎች የበላይ አመራሮች እና ከሰላም ሚንስትር ጋር በጋራ በመሆን በራያና አካባቢው የሰላም ጉዳይ ውይይት አካሄዱ::

በውይይታቸውም ማንኛውም አይነት ጥያቄ በሰላማዊ መንገድ ብቻ እንዲቀርብና እንዲስተናገድ ስምምነት ላይ ደርሰዋል::

በዚህም መሰረት በራያም ሆነ በሌሎች አካባቢዎች ከማንነትም ሆነ ከሌሎች ጉዳዮች ጋር በተያያዘ የሚነሳ ጥያቄ ሕገ-መንግስቱንና ህዝቡን ማዕከል ባደረገ መንገድ ሊፈታ እንደሚገባው: ከዚህ ውጪ የሚደረግ እንቅስቃሴ ተቀባይነት እንደሌለው አመራሮቹ አስምረውበታል::

በፌዴራልም ሆነ በክልል የሚገኙ የመንግስትም ሆነ የግል የመገናኛ ብዙሀን በሁለቱ ክልሎች መካከል ይበልጥ መግባባትና መቀራረብ እንዲፈጠር በኃላፊነት መንፈስ መስራት እንዳለባቸውም አሳስበዋል::

በነገው ዕለት በተለያዩ የክልላችን ልዩ ልዩ ከተሞች የማንነት ጥያቄዎች ሰላማዊ በሆነ ሁኔታ እንዲፈቱ፣ ላሊበላን እና ጣናን መታደግ እንደሚገባ መልዕክት ለማስተላለፍ ጥያቄዎች ቀርበው ምላሽ ተሰጥቷል::

በዚህ አጋጣሚ ሰልፎቹ ሰላማዊ ሆነው እንዲጠናቀቁ ለሁሉም ወገኖች የጥንቃቄ መልዕክት እናስተላልፋለን ::

አቶ ንጉሱ ጥላሁን

No comments