Latest

ከወልቃይት ጠገዴ የተፈናቀሉ ወጣቶች በአዲስ አበባ - [ጋዜጠኛ ጌታቸው ሽፈራው]

ከወልቃይት ጠገዴ የተፈናቀሉ ወጣቶች በአዲስ አበባ

ከወልቃይት ጠገዴ የተፈናቀሉ ወጣቶች በዚህ መልክ አብን ቢሮ ይገኛሉ። ወጣቶቹ ወደ አዲስ አበባ ሲመጡ ፍትህ እናገኛለን ብለው ነበር።  


ሆኖም የፌደራልና የአዲስ አበባ ፖሊስ የአብንን ቢሮ ከብቦ ወጥተው አቤቱታቸውን እንዳያሰሙ አግዷቸዋል። "ከወጡ እንተኩሳለን" እያለ መዛቱ ተገልፆአል።

ለወጣቶቹ ተራ ጀሮ ጠቢና ፖሊስ መላኩ አይደለም የሚገርመው። አንድ ከሰራዊቱ የወጣና በየጋዜጣው "ሪፎርም ያስፈልጋል" ሲል የምናውቀው ጀኔራልም ሁኔታውን ለማየት በቢሮው በኩል ሲያልፍ ተመልከቻለሁ። እንግዲህ የትህነግን ሰላዮች ስምሪት የሚቆጣጠረውና ወደ መቀሌ ሪፖርት የሚያጠናቅረው ይህ ጀኔራል ይሆናል።
ከወልቃይት ጠገዴ የተፈናቀሉ ወጣቶች በአዲስ አበባ
ወልቃይት ጠገዴ 1983 ዓ.ም በትግራይ መንግስት በኃይል መያዙ ይታወሳል፡፡ የትግራይ መንግስት ወልቃይት ጠገዴ የማንንት ጥያቄ ባቀረቡ የወልቃይት አማራዎች ላይ አስር፤ሰቆቃ፣ ግድያ ሲፈፀም ቆይቷል፡፡

የትግራይ መንግስት አማራዎችን በማፈናቀል በአንፃሩ የህዝቡን ስብጠር ለመቀየር ትግሬዎችን ከአድዋ፣ ከአድግራት፣ ከአንደርታ፣ ከአክሱም… ወዘተ በማምጣት በወልቃይት ለም መሬቶች ላይ አስፍሯል፡፡

በአካባቢው የትግራይ መንግስት በዘረጋው የአፈና መዋቅር የወልቃይት ጠገዴ አማራ ተወላጅ ላይ የተጠና አስተዳደራዊ በደል እየፈፀመ ይገኛል፡፡ ከወልቃይት ጠገዴ የተፈናቀሉ ወጣቶች በአዲስ አበባ
የኢፌድሪ ጠቅላይ ሚኒስቴርም እየተፈፀመ ያለውን በደል እንዲረዳና አስቸኳይ መፍትሔ እንዲሰጠን የሚከተሉትን ዋና ዋና ጥያቀዎቻችን እናቀርባለን፡፡

  • የትግራይ መንግስት በወልቃይት ጠገዴ አማራ ላይ የሚፈፅመውን ግድያ፣ አፈና፣ሰቆቃ፣አስር እና መፈናቀል በአስቸኳይ እንዲያቆም 
  • የወልቃይት ጠገዴ አማራዋች በቋንቋችን በአማርኛ የመናገር የመማር የመፃፍ፤በበህላችን ሀዘንና ደስታችን የመግለፅ መብታችን አንዲከበር
  • በትግራይ መንግስት የሚፈፀም የመሬት ዝርፊያ እንዲቆምልን እና ሐብት ንብረት የማፍራት መብታችን እንዲረጋገጥ
  • በማንነታቸው ምክንያት ከወልቃይት ጠገዴ ተፈናቅለው ሶሮቃ ጎንደር አዲስ አበባ በጊዚያዊ መጠለያ የሚገኝ የወልቃይት ጠገዴ አማራዎች በአስቸኳይ ወደ ትውልድ ቀያቸው እንዲመለሱና የተረጋጋ ሕይወት እንዲመሩ እንዲደረግ

  • ትግራይ ፀጥታ አካላት ወልቃይት ጠገዴን ለቀው እንዲወጡ እና የፌደርል የፀጥታ አካላት በቦታው እንዲተኩ እንዲደረግ
  • የወልቃይት ጠገዴ አማራ ማነንነት ጥያቄ በአስቸኳይ እንዲመለስ 
  • ወደ ወልቃይት ጠገዴ የመጡ የትግራይ ሰፋሪዎች በማንነታችን ጥያቄ ላይ የሚፈፅሙትን ሴራና ደባ እንዲቆሙልን
ለወጣቶቹ ድጋፍ ማድረግ የምትፈልጉ አራት ኪሎ ግንፍሌ ከድልድዩ ወደ ጃንሜዳ በሚወስደው መንገድ በኩል የሚገኘው የአብን ቢሮ በመሄድ ማገዝ ትችላላችሁ።
ከወልቃይት ጠገዴ የተፈናቀሉ ወጣቶች በአዲስ አበባ

ከወልቃይት ጠገዴ የተፈናቀሉ ወጣቶች በአዲስ አበባ

ከወልቃይት ጠገዴ የተፈናቀሉ ወጣቶች በአዲስ አበባ

No comments