Latest

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ የልማት ተቋም አማካሪ ምክር ቤት መግለጫ

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ

የኢትዮጵያ ዳያስፖራ የልማት ተቋም አማካሪ ምክር ቤት (ምክር ቤት) የኢትዮጵያ ጠቅላይ ሚኒስቴር ጽ /ቤት እ.ኤ.አ. ነሐሴ 9 ቀን 2018 ዓ.ም ባወጣው መግለጫ መሰረት በማድረግ የኢትዮጵያ ዲያስፖራ በልማት ተሳትፎ ጥረቶችን ለማበረታታትና ለማስተባበር ዝግጁ መሆኑን በደስታ ይገልፃል።

በተለያዩ አጋጣሚዎች ጠቅላይ ሚኒስትር ዶ / ር አቢ አህመድ የዲያስፖራ ኢትዮጵያውያን በዩኤስ 1ዶላር በመለገስ በኢትዮጵያ ወሳኝ አስፈላጊና ያልተሟላ የልማት ፍላጎቶችን እንዲያሙዋሉ ጠይቋል. በተጨማሪም እንዳሉት የታቀደው የልማት ገንዘብ “የመንግስት በጀት አካል አይሆንም። በራሱ በራሱ ቦርድ ይተገበራል።”

ለጠቅላይ ሚኒስትር ዶ/ር አብይ ተግዳሮት ምላሽ በኢትዮጵያ ዲያስፖራ ውስጥ ከፍተኛ አጠቃላይ አዎንታዊ አግኝቷል። የካውንስሉ አባላት ለተዋጣው ስኬታማ ውጤት ለማረጋገጥ የተለያዩ ልዩ ልዩ እውቀታቸውን እና ችሎታቸውን በመጠቀም ይጥራሉ።  


ይህ በጠቅላይ ሚኒስትር አቢይ አህመድ እና አማካሪ ካውንስል ብቻ የሚያከናዉኑት ነገር አይደለም። ነገር ግን ሁላችንም ሀገራችንን ለማገልገል ባደረግነው ጥረቶች እና ግዴታዎች የሚወሰን ነው። በቅርቡ ምክር ቤቱ ተጨማሪ አባላት ስራዉን ለመርዳት ይሰየማሉ።

ካውንስሉ አንደኛው ትኩረት የሚሰጠው ወሳኝ ተግባር ለድርጅቱ ሁሉን አቀፍ ጠንካራ ተጠያቂነት እና ግልጽነት አሰራር ስነስርዓት መዘርጋት ነው። ለዚህም ገንዘቡን የሚያበረክቱት አስተዋፅኦዎች ተጠቃሚዎች እና ሌሎች ባለድርሻዎች ስለ ፈንዱ አስተዳደርና አስተገባበር ያላቸዉን አስተሳሰብ ለማካተት ይጥራል።

የዲያስፖራው ኢትዮጵያውያኞች አንዳንድ ቦታ ለምን አሁኑኑ ገንዘብ መዋጮ አንሰጥም የሚል ጥያቄ ያነሳሉ።

ካውንስሉ ስለፈንዱ ለኢትዮጵያ ዲያስፖራው አንዳንድ የህግ እና የቁጥጥር እውነታዎች እንዲያውቅ ይፈልጋል።

በዲያስፖራው ኢትዮጵያውያን ለሚያደርጉት አስተዋፅኦ ከፍተኛውን የተጣራ ገቢ እንዲኖር በዓለም ዙሪያ ከበርካታ የፋይናንስ ተቋማት ጋር አሰራር ዘዴ እያመቻቸን ነው። 

ይህንን የምናደርገው የኢትዮጵያን ጨምሮ ለሁሉም ሀገራት ሕጋዊ መስፈርቶች መሟላት በማረጋገጥ ለሀገሪቷ ትክክለኛ ሂደቶች እና መቆጣጠሪያዎች መኖራቸውን ለማረጋገጥ ነው። ይህ ቅንብር በቅርብ ጊዜ ባስቸኳይ መደረግ እንዳለበት ካዉንስሉ ይረዳል። ይህን ለማድረግ ትንሽ ጊዜ ስለሚጠይቅ የኢትዮጵያ ዲያስፖራዎችን ትዕግስት እንጠይቃለን።

ካውንስሉ የአሜሪካ ፌዴራል እና የግዛት ህጎችን ማሟላት አለበት። እንዲሁም የበጎ አድራጎት ድርጅቶች ክዋኔዎችን ለማስተዳደር የወጡትን ድነጋጌዎች ማሟላት ያስፈለገዋል።

ካውንስሉ ለድርጅቱ የአስተዳደር መዋቅሮችን እና ሂደቶችን ጨምሮ ሌሎች የተለያዩ ተግባራትን እያከናወነ ነው። የዲያስፖራው የኢትዮጵያ ህብረተሰብ በትዕግስት ከእኛ ጋር መቆየቱን እንዲቀጥል እንጠይቃለን። በተቻለ ፍጥነት ሁሉንም ስራ ለመስራት ዝግጁ ነን።

ምክር ቤቱ በቀጣዩ ወር መግለጫ እስኪሰጥ ድረስ የኢትዮጵያውያን ዲያስፖራ ደጋፊዎች ወርሃዊ መዋጮ ለመስጠት ያቀዱትን ለጊዜው እንዲይዙ በአክብሮት ይጠይቃል።

ምክር ቤቱ በየጊዜው በድረገፅና በሌሎች የመገናኛ ዘዴዎች ኦፊሴላዊ መረጃዎችን ይሰጣል።

ካውንስሉ የተለያዩ ግለሰቦች እና ቡድኖችን የግል ገንዘብ መዋጮ ለፈንዱ ለመሰብሰብ እንደተሰማሩ ያውቃል። ነገር ግን እነዚህ ግለሰቦችም ሆኑ ድርጅቶች ከካዉንስሉ ጋር የሚሰሩ አይደሉም። ወደፊት ፈንዱ መተገበር ሲጀምር ከካዉንስሉ ጋር እንደሚተባበሩ ተስፋ እናደርጋለን።

ምክር ቤቱ በመጀመሪያ ጊዜ ጥራት ያለው ስራ መስራት ይሻላል ወደህዋላ ተመለሶ ከመጠገን በሚለው ሃሳብ ይመራል። ኮሚሽኑ ለመላው የኢትዮጵያ ዲያስፖራ ፈንዱን ለመደገፍ ላሳዩት ከፍተኛ ጉጉት ድጋፍና በጎ ፈቃድ ምስጋናዉን ያቀርባል።

የካውንስሉ ሰብሳቢ ዶ/ር አለማየሁ ገብረማርያም
እውቅያ: EDTF2018@gmail.com

No comments